am_tw/bible/names/peter.md

1.1 KiB

ጴጥሮስ፣ ስምዖን ጴጥሮስ፣ ኬፋ

እነዚህ ስሞች ከአሥራ ሁለቱ የኢየሱስ ሐዋርያት አንዱ የነበረው የጴጥሮስ መጠሪያዎች ናቸው። በጥንት ቤተ ክርስቲያን ታዋቂ መሪ ነበር።

  • ኢየሱስ እርሱን ከመጥራቱ በፊት ይህ ሰው ስምዖን ይባል ነበር።
  • በኋላ ላይ ኢየሱስ፣ ኬፋ በማለትም ጠርቶታል፤ ይህም በአረማይክ ቋንቋ “ድንጋይ” ወይም፣ “ዐለት” ማለት ነው። ጴጥሮስ ተብሎም ተጠርቷል፤ ይህም በግሪክ ቋንቋ “ድንጋይ” ወይም፣ “ዐለት” ማለት ነው።
  • በጣም የሚታወቀው ጴጥሮስ ወይም ስምዖን ጴጥሮስ በተሰኘው ስሙ ነው።
  • ሰዎችን ለመፈወሰና የኢየሱስን የምሥራች ቃል ለመስበክ እግዚአብሔር በጴጥሮስ ተጠቅሟል።
  • አማኝ ወገኖችን ለማበረታታትና ለማስተማር ጴጥሮስ አዲስ ኪዳን ውስጥ ያሉትን ሁለት መልእክቶች ጽፏል።