10 lines
1.1 KiB
Markdown
10 lines
1.1 KiB
Markdown
|
# ጴጥሮስ፣ ስምዖን ጴጥሮስ፣ ኬፋ
|
||
|
|
||
|
እነዚህ ስሞች ከአሥራ ሁለቱ የኢየሱስ ሐዋርያት አንዱ የነበረው የጴጥሮስ መጠሪያዎች ናቸው። በጥንት ቤተ ክርስቲያን ታዋቂ መሪ ነበር።
|
||
|
|
||
|
* ኢየሱስ እርሱን ከመጥራቱ በፊት ይህ ሰው ስምዖን ይባል ነበር።
|
||
|
* በኋላ ላይ ኢየሱስ፣ ኬፋ በማለትም ጠርቶታል፤ ይህም በአረማይክ ቋንቋ “ድንጋይ” ወይም፣ “ዐለት” ማለት ነው። ጴጥሮስ ተብሎም ተጠርቷል፤ ይህም በግሪክ ቋንቋ “ድንጋይ” ወይም፣ “ዐለት” ማለት ነው።
|
||
|
* በጣም የሚታወቀው ጴጥሮስ ወይም ስምዖን ጴጥሮስ በተሰኘው ስሙ ነው።
|
||
|
* ሰዎችን ለመፈወሰና የኢየሱስን የምሥራች ቃል ለመስበክ እግዚአብሔር በጴጥሮስ ተጠቅሟል።
|
||
|
* አማኝ ወገኖችን ለማበረታታትና ለማስተማር ጴጥሮስ አዲስ ኪዳን ውስጥ ያሉትን ሁለት መልእክቶች ጽፏል።
|