am_tw/bible/names/gilead.md

577 B

ገለዓድ

ገለዓድ የጋድ፣ የሮቤልና የምናሴ ነገዶች የነበሩበት ከዮርዳኖስ ወንዝ ምሥራቅ የነበረ ተራራማ አካባቢ ስም ነው።

  • አካባቢው ከነበረው ኮረብታማ ተፈጥሮ የተነሣ “ኮረብታማው የገለዓድ አገር” ወይም፣ “የገለዓድ ተራራ” ተብሎ ይጠራ ነበር።
  • ብሉይ ኪዳን ውስጥ ገለዓድ ተብለው የተጠሩ ጥቂት ሰዎች አሉ። ከእነርሱም አንድ የምናሴ የልጅ ልጅ ነው።