am_tw/bible/names/benjamin.md

9 lines
637 B
Markdown

# ብንያም
ብንያም ከያዕቆብና ከሚስቱ ከራሔል የተወለደ የመጨረሻው ልጅ ነው። የስሙ ትርጉም ፥ “የቀኝ እጄ ልጅ” ማለት ነው።
* ከራሔል የተወለዱ እርሱና ታላቅ ወንድሙ ዮሴፍ ብቻ ናቸው። ራሔል ብንያምን ከወለደች በኋላ ሞታለች
* የብንያም ዘሮች ከአስራሁለት የእስራኤል ነገዶች አንዱ ሆነዋል
* ንጉሥ ሳኦል ከእስራኤላዊው የብንያም ነገድ የተገኘ ነበር
* ሐዋርያው ጳውሎስም ከብንያም ነገድ ነበር