am_tw/bible/names/benjamin.md

637 B

ብንያም

ብንያም ከያዕቆብና ከሚስቱ ከራሔል የተወለደ የመጨረሻው ልጅ ነው። የስሙ ትርጉም ፥ “የቀኝ እጄ ልጅ” ማለት ነው።

  • ከራሔል የተወለዱ እርሱና ታላቅ ወንድሙ ዮሴፍ ብቻ ናቸው። ራሔል ብንያምን ከወለደች በኋላ ሞታለች
  • የብንያም ዘሮች ከአስራሁለት የእስራኤል ነገዶች አንዱ ሆነዋል
  • ንጉሥ ሳኦል ከእስራኤላዊው የብንያም ነገድ የተገኘ ነበር
  • ሐዋርያው ጳውሎስም ከብንያም ነገድ ነበር