9 lines
1.2 KiB
Markdown
9 lines
1.2 KiB
Markdown
# ጋኔን፣ ክፉ መንፈስ፣ ርኵሳን መናፍስት
|
|
|
|
እነዚህ ሁሉ የሚያመለክቱት አጋንንትን ሲሆን፣ አጋንንት የእግዚአብሔርን ፈቀድ የሚቀወሙ መንፈሳዊ ፍጥረቶች ናቸው።
|
|
|
|
* እርሱን እንዲያገለግሉ እግዚአብሔር መላእክትን ፈጠረ። ዲያብሎስ በእግዚአብሔር ላይ ሲያምጽ ከመላእክቱም ጥቂቶቹ በማመጻቸው ከሰማይ ተጣሉ። አጋንንትና ክፉ መናፍስት፣ “እነዚህ የተጣሉ” መላእክት እንደ ሆኑ ይታሰባል።
|
|
* እነዚህ አጋንንት አንዳንዴ፣ “ርኵሳን መናፍስት” ተብለው ይጠራሉ። “ርኵስ” “ንጹሕ ያልሆነ” ወይም፣ “ክፉ” ወይም፣ “ቅዱስ ያልሆነ” ማለት ነው።
|
|
* አጋንንት የሚያገለግሉት ዲያብሎስን ስለ ሆነ ክፉ ነገር ያደርጋሉ። አንዳንድ ጊዜ እነርሱ ውስጥ በመግባት ሰዎችን ይቆጣጠራሉ።
|
|
* አጋንንት ከሰው የበለጠ ብርቱ ቢሆኑም፣ የእግዚአብሔርን ያህል ግን ብርቱ አይደሉም።
|