am_tw/bible/kt/boast.md

1.4 KiB

መመካት፣ ትምክህተኛ

“መመካት” በሰዎች ወይም በነገሮች በመመካት በትዕቢት መናገር ማለት ነው። ብዙውን ጊዜ ስለ አራስ በእብሪት መናገር ማለት ነው።

  • “ትምክህተኛ” ሰው ስለ ራሱ በትዕቢት ይናገራል።
  • በጣዖቶቻቸው በመመካታቸው እግዚአብሔር እስራኤላውያንን ገሥጾአል። በእውነተኛው አምላክ ይልቅ በግትርነት ጣዖቶቻቸውን እያመለኩ ነበር።
  • መጽሐፍ ቅዱስ ሀብትን፣ ብርታትን፣ ፍሬያማ እርሻንና ሕጎቻቸውን በመሳሰሉ ነገሮች ስለሚመኩ ሰዎችም ይናገራል። ይህም ማለት እነዚህን ነገሮች የሚሰጥ እግዚአብሔር መሆኑን ከመገንዘብ ይልቅ፣ በእነዚህ ነገሮች ትዕቢት አድሮባቸዋል ማለት ነው።
  • በእነዚህ ነገሮች ከመመካት ወይም ከመታመን ይልቅ እርሱን በማወቃቸው እንዲመኩ እግዚአብሔር አጥብቆ ለእስራኤላውያን ተናግሮአል።
  • ሐዋርያው ጳውሎስ በጌታ ስለ መመካት ይናገራል፤ ይህም ማለት እርሱ ስላደረገላቸው ሁሉ በእርሱ ደስ መሰኘትና እርሱን ማመስገን ማለት ነው።