am_tw/bible/other/word.md

1.1 KiB

ቃል

“ቃል” አንድ ሰው የተናገረውን ያመለክታል።

  • ለዚህ ምሳሌ የሚሆነን፣ “ቃሌን አላመንህምና” በማለት መልአኩ ለዘካርያስ የተናገረው ነው፤ እንዲህ ማለቱ፣ “የነገርሁህን አላመንህም” ማለቱ ነበር።
  • አብዛኛውን ጊዜ ይህ አንድን ቃል ብቻ ሳይሆን መላውን መልእክት ያመለክታል።
  • ብዙውን ጊዜ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “ቃል”እግዚአብሔር የተናገረውን ወይም ያዘዘውን ሁሉ ይመለከታል፤ “የእግዚአብሔር ቃል” ወይም፣ “የእውነት ቃል” እንደ ተሰኙት።
  • አንዳንዴ፣ “ቃል” አጠቃላዩን ንግግር ያመለክታል፣ ለምሳሌ፣ “በቃልና በሥራ የበረታ እንደሚለው። ይህ “በንግግሩም ሆነ በጸባዩ ብርቱ የሆነ” ማለት ነው።
  • ይህ ቃል በጣም በተለየ ሁኔታ ጥቅም ላይ የዋለው ኢየሱስ፣ “ቃል” በመባሉ ነው።