1.2 KiB
1.2 KiB
ያልተፈቀደ
“ያልተፈቀደ” ነገር የሚያደርግ ሰው ሕግ ያፈርሳል።
- አዲስ ኪዳን ውስጥ፣ “ያልተፈቀደ” የሚለው ቃል ጥቅም ላይ የዋለው፣ የእግዚአብሔርን ሕግ ማፍረስን ብቻ ሳይሆን ሰው ሠራሽ የአይሁድ ሕግንም ለማፍረስ ጭምር ነው።
- በጊዜ ውስጥ አይሁድ እግዚአብሔር በሰጣቸው ሕግ ላይ የራሳቸውንም ጨምረዋል። ከእነርሱ ሰው ሠራሽ ሕግ ጋር የማይስማማውን አይሁድ፣ “ያልተፈቀደ” ይሉታል።
- ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱ በሰንበት ቀን እሸት ቀጥፈው በመብላታቸው፣ በዚያ ቀን ምንም ነገር እንዳይደረግ የደነገገውን የአይሁድ ሕግ ማፍረስ በመሆኑ፣ “ያልተፈቀደ” ብለውታል።
- ንጹሕ ያልሆነ ምግብ መብላት ለእርሱ፣ “ያልተፈቀደ” እንደ ነበር ጴጥሮስ ሲናገር ይህን ምግብ ከበላ አንዳንድ ምግቦችን እንዳይበሉ እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን የሰጠውን ሕግ ማፍረስ መሆኑን ማመልከቱ ነበር።