am_tw/bible/other/unlawful.md

9 lines
1.2 KiB
Markdown
Raw Permalink Normal View History

2021-03-04 19:07:37 +00:00
# ያልተፈቀደ
“ያልተፈቀደ” ነገር የሚያደርግ ሰው ሕግ ያፈርሳል።
* አዲስ ኪዳን ውስጥ፣ “ያልተፈቀደ” የሚለው ቃል ጥቅም ላይ የዋለው፣ የእግዚአብሔርን ሕግ ማፍረስን ብቻ ሳይሆን ሰው ሠራሽ የአይሁድ ሕግንም ለማፍረስ ጭምር ነው።
* በጊዜ ውስጥ አይሁድ እግዚአብሔር በሰጣቸው ሕግ ላይ የራሳቸውንም ጨምረዋል። ከእነርሱ ሰው ሠራሽ ሕግ ጋር የማይስማማውን አይሁድ፣ “ያልተፈቀደ” ይሉታል።
* ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱ በሰንበት ቀን እሸት ቀጥፈው በመብላታቸው፣ በዚያ ቀን ምንም ነገር እንዳይደረግ የደነገገውን የአይሁድ ሕግ ማፍረስ በመሆኑ፣ “ያልተፈቀደ” ብለውታል።
* ንጹሕ ያልሆነ ምግብ መብላት ለእርሱ፣ “ያልተፈቀደ” እንደ ነበር ጴጥሮስ ሲናገር ይህን ምግብ ከበላ አንዳንድ ምግቦችን እንዳይበሉ እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን የሰጠውን ሕግ ማፍረስ መሆኑን ማመልከቱ ነበር።