1.2 KiB
1.2 KiB
ስቃይ
“ስቃይ” የሚያመለክተው ከፍተኛ መከራን ነው። አንድን ሰው ማሰቃየት ብዙውን ጊዜ በጭካኔ ከባድ መከራ እንዲደርስበት ማድረግ ነው።
- አንዳንዴ፣ “ስቃይ” አካላዊ ሕመምና መከራን ያመለክታል። ለምሳሌ፣ የዮሐንስ ራእይ አውሬውን በሚያመልኩ ሰዎች ላይ በመጨረሻው ዘመን ስለሚደርሰው ስቃይ ይገልጻል።
- መከራ ኢዮብ ላይ እንደ ደረሰው መንፈሳዊና ስሜታዊ ይዘት ሊኖረውም ይችላል።
- የዮሐንስ ራእይ እንደሚነግረን እንደ አዳኝ በኢየሱስ የማያምኑ ሰዎች የእሳት ባሕር ውስጥ ዘላለማዊ መንፈሳዊ ስቃይ ይቀበላሉ።
- ይህ ቃል፣ “ከባድ መከራ” ወይም፣ “አንድን ሰው በጣም ማሳመም ወይም፣ “ጭንቀት” በማለት መተርጎም ይቻላል።
- ትርጕሙን ይበልጥ ግልጽ ለማድረግ፣ “አካላዊ” ወይም፣ “መንፈሳዊ” የሚል ቃል መጨመር ያስፈልግ ይሆናል።