am_tw/bible/other/snare.md

1.8 KiB

ወጥመድ፣ አሽከላ

“ወጥመድ” እና፣ “አሽከላ” የተሰኙት ቃሎች እንስሶችን ለመያዝና ከዚያ እንዳያመልጡ ለመድረግ ጥቅም ላይ የሚውሉ ነገሮች ናቸው። የሚጠመደውን እንስሳ በድንገት እንደያዘው ብዙውን ጊዜ ወጥመዱ ወይም አሽክላው ድብቅ ቦታ ላይ ይቀመጣል

  • በመንፈሳዊ መልኩ አንድን ሰው ማጥመድን አስመልክቶ እነዚህ ቃሎች በምሳሌነት ጥቅም ላይ ይውላሉ
  • ብዙውን ጊዜ ወጥመድ እንስሳው ሲረግጠው እግሩን ለመያዝ በድንገት የሚጠብቅ የገመድ ወይም የሽቦ ሸምቀቆ ይኖረዋል
  • ብዙውን ጊዜ ወጥመድ የሚሰራው ከብረት ወይም ከእንጨት ሲሆን የእንስሳውን አንድ አንድ አካል ክፍል በፍጥነትና በኅይል ለመያዝ እርስ በርስ የሚገጣጠሙ ሁለት ክፍሎች አሉት’
  • ኅጢአትና ፈተና ሰዎችን እንደሚያጠምድ ወጥመድ መሆናቸውን ለማመልከት መጽሐፍ ቅዱስ በእነዚህ ቃሎች ይጠቅማል
  • ሰዎች ኅጥአትን እንዲፈጽሙ ለማነሳሳት ሰይጣንና ክፉ ሰዎች ወጥመድ እንደሚዘረጉ መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል
  • “ወጥመድ መዘርጋት” ሌላውን ለመያዝ በፍጥነት እንዲዘጋ ወጥመድ ማዘጋጀት ማለት ነው
  • “ወጥመድ ውስጥ መውደቅ” እንድ ሰው ውስጥ እንዲወድቅ ታስቦ የተቆፈረ ጉድጓድ ወይም ጉድባ ውስጥ መውደቅን ያመለክታል
  • በኅጢአት ወጥመድ መያዝ ወይም መጠመድ አደገኛ ውጤት ያስከትላል