13 lines
1.8 KiB
Markdown
13 lines
1.8 KiB
Markdown
|
# ወጥመድ፣ አሽከላ
|
||
|
|
||
|
“ወጥመድ” እና፣ “አሽከላ” የተሰኙት ቃሎች እንስሶችን ለመያዝና ከዚያ እንዳያመልጡ ለመድረግ ጥቅም ላይ የሚውሉ ነገሮች ናቸው። የሚጠመደውን እንስሳ በድንገት እንደያዘው ብዙውን ጊዜ ወጥመዱ ወይም አሽክላው ድብቅ ቦታ ላይ ይቀመጣል
|
||
|
|
||
|
* በመንፈሳዊ መልኩ አንድን ሰው ማጥመድን አስመልክቶ እነዚህ ቃሎች በምሳሌነት ጥቅም ላይ ይውላሉ
|
||
|
* ብዙውን ጊዜ ወጥመድ እንስሳው ሲረግጠው እግሩን ለመያዝ በድንገት የሚጠብቅ የገመድ ወይም የሽቦ ሸምቀቆ ይኖረዋል
|
||
|
* ብዙውን ጊዜ ወጥመድ የሚሰራው ከብረት ወይም ከእንጨት ሲሆን የእንስሳውን አንድ አንድ አካል ክፍል በፍጥነትና በኅይል ለመያዝ እርስ በርስ የሚገጣጠሙ ሁለት ክፍሎች አሉት’
|
||
|
* ኅጢአትና ፈተና ሰዎችን እንደሚያጠምድ ወጥመድ መሆናቸውን ለማመልከት መጽሐፍ ቅዱስ በእነዚህ ቃሎች ይጠቅማል
|
||
|
* ሰዎች ኅጥአትን እንዲፈጽሙ ለማነሳሳት ሰይጣንና ክፉ ሰዎች ወጥመድ እንደሚዘረጉ መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል
|
||
|
* “ወጥመድ መዘርጋት” ሌላውን ለመያዝ በፍጥነት እንዲዘጋ ወጥመድ ማዘጋጀት ማለት ነው
|
||
|
* “ወጥመድ ውስጥ መውደቅ” እንድ ሰው ውስጥ እንዲወድቅ ታስቦ የተቆፈረ ጉድጓድ ወይም ጉድባ ውስጥ መውደቅን ያመለክታል
|
||
|
* በኅጢአት ወጥመድ መያዝ ወይም መጠመድ አደገኛ ውጤት ያስከትላል
|