am_tw/bible/other/selah.md

684 B

ሴላ

ሴላ ብዙውን ጊዜ መዝሙር መጽሐፍ ውስጥ የሚገኝ የዕብራይስጥ ቃል ነው በርካታ ትርጉሞች ይኖሩት ይሆናል

  • ጉባኤው የተነገረውን ረጋ ብሎ እንዲያስብ ጥሪ ለማቅረብ የታሰበ፣ “ረጋ በል፤ አመስግን” ማለት ሊሆን ይችላል
  • መዝሙሮቹ የተጻፉት በጉባኤ እንዲዘመሩ በመሆኑ ዘማሪው ዝም እንዲልና የሙዚቃ መሣሪያው ብቻ እንዲጫወት ወይም አዳማጮቹ የመዝሙሩን ቃሎች በሚገባ እንዲያስቡ የሚያመለክት ሙዚቃዊ ቋንቋ ሊሆን ይችላል