ሴላ
ሴላ ብዙውን ጊዜ መዝሙር መጽሐፍ ውስጥ የሚገኝ የዕብራይስጥ ቃል ነው በርካታ ትርጉሞች ይኖሩት ይሆናል
- ጉባኤው የተነገረውን ረጋ ብሎ እንዲያስብ ጥሪ ለማቅረብ የታሰበ፣ “ረጋ በል፤ አመስግን” ማለት ሊሆን ይችላል
- መዝሙሮቹ የተጻፉት በጉባኤ እንዲዘመሩ በመሆኑ ዘማሪው ዝም እንዲልና የሙዚቃ መሣሪያው ብቻ እንዲጫወት ወይም አዳማጮቹ የመዝሙሩን ቃሎች በሚገባ እንዲያስቡ የሚያመለክት ሙዚቃዊ ቋንቋ ሊሆን ይችላል