am_tw/bible/other/obey.md

1.1 KiB

መታዘዝ፣ ታዛዥ፣ ታዛዥነት

“መታዘዝ” ሥልጣን ያለው ሰው የሚፈልገውን ወይም እንዲደረግ የሚያዝዘውን መፈጸም ማለት ነው። “ታዛዥ” የተነገረውን ወይም የታዘዘውን የሚፈጽም ሰው ነው።

  • ሰዎች የአገር መሪዎች መንግሥት ወይም ድርጅት ለሚያወጧቸው ሕጎችም ይታዘዛሉ።
  • ልጆች ለወላጆቻቸው ይታዘዛሉ፣ ባርያዎች ለጌቶቻቸው ይታዘዛሉ፤ ሰዎች ለእግዚአብሔር ይታዘዛሉ፤ ዜጎች ለአገራቸው ሕጎችና ደንቦች ይታዘዛሉ።
  • ሕጉ ወይም ሥልጣን ያለው ሰው አንድ ነገር እንዳይደረግ ካዘዙ፣ ሰዎች ያንን ላለማድረግ መታዘዝ አልባቸው።
  • ይህን ቃል ለመተርጎም የሚጠቅሙ ቃሎች ወይም ሐረጎች፣ “የታዘዘውን ማድረግ” ወይም፣ “ትእዛዙን መከተል” ወይም፣ “እግዚአብሔር የተናገረውን ማድረግ” የተሰኙትንም ያካትታል።