am_tw/bible/other/member.md

926 B

ብልት፣ ክፍል

ብልት ወይም ክፍል የአንድ ሕንፃ፣ አካል ወይም ቡድን አንድን ክፍል ያመለክታል።

  • አዲስ ኪዳን ክርስቲያኖችን የክርስቶስ አካል፣ “ብልቶች” ይላቸዋል። በክርስቶስ የሚያምኑ ከተለያዩ ብዙ ብልቶች የተሠራው አካል ወገን ናቸው።
  • ኢየሱስ ክርስቶስ የአካሉ፣ “ራስ” ሲሆን እያንዳንዱ አማኝ እንደ አካሉ ብልቶች ይሠራሉ። መላው አካል በሚገባ መሥራት እንዲችል መንፈስ ቅዱስ ለእያንዳንዱ የአካሉ ብልት ትክክለኛ ቦታውን ይሰጠዋል።
  • የአይሁድ ሸንጎና የፈሪሳውያንን በመሳሰሉ ቡድኖች ውስጥ ተሳትፎ ያላቸው ግለ ሰቦች የእነዚያ ቡድኖች “ብልቶች” ተብለዋል።