am_tw/bible/other/lute.md

906 B

ክራር፣ መሰንቆ

ክራርና መሰንቆ እስራኤላውያን እግዚአብሔርን ለማምለክት የሚጠቀሙባቸው ትናንሽ ባለ ገመድ የሙዚቃ መሣሪያዎች ናቸው።

  • መሰንቆ ክሮቹ የሚወጠሩበት ቀዳዳ ያሉት በመሆኑ በጣም በገናን ይመስላል።
  • ክራር የድምፅ እንጨት ሳጥንና ክሮቹ የሚወጠሩበት ረዘም ያለ አንገት ስላለው በብዙ መልኩ የዘመኑን ጊታር ይመስላል።
  • ክራር ወይም መሰንቆ ለመጫወት ሲፈለግ አንዳንድ ክሮች ጫን ተደርገው በጣቶች ሲያዙ፣ ሌሎች ደግም በሌላ እጅ ይመታሉ።
  • የክሮቹ ቁጥር የተለያየ ቢሆንም፣ ብሉይ ኪዳን በተለይ አሥር ክሮች (አውታር) ስላሉት መሣሪያዎች ይናገራል።