am_tw/bible/other/interpret.md

1.4 KiB

መተርጎም፣ ትርጉም

“መተርጎም” እና፣ “ትርጉም” የተሰኙት ግልጽ ያልሆነ ነገርን መርዳትና ያንን ግልጽ ማድረግን ያመለክታል።

  • መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እነዚህ ቃሎች ብዙውን ጊዜ ጥቅም ላይ የዋሉት የሕልምን ፍቺ ግልጽ ከማድረግ ጋር በተያያዘ ነው።
  • የባቢሎን ንጉሠአንዳንድ ግራ የሚያጋቡ ሕልሞች ባለመ ጊዜ ምን ማለት እንደሆኑ እንዲተረጉምና ግልጽ እንዲያደርግ እግዚአብሔር ዳንኤልን ረዳው።
  • የሕልሙ “ትርጉም”፣ የሕልሙን መልእክት ግልጽ ማድረግ ነው። አንዳንዴ እነዚህ ትርጉሞች በጽሑፍ ይሰፍራሉ።
  • ከብሉይ ኪዳን እንደምንመለከተው ብዙ ጊዜ እግዚአብሔር ወደፊት የሚሆኑ ነገሮችን ለሰዎች በሕልም ይገልጽ ነበር፤ ስለሆነም የእነዚህ ሕልሞች ትርጉም ትንቢት ነበር ማለት ነው።
  • “መተርጎም” የሚለው ቃል በተፈጥሮአዊው ዓለም እየሆን ያለውን መሠረት በማድረግ የአየሩ ሁኔታ ምን ሊሆን እንደሚችል መገመትን የመሰለ የአንዳንድ ነገሮችን ምንነት መገመትን ለምግለጽም ጥቅም ላይ ይውላል።