am_tw/bible/other/festival.md

1.0 KiB

በኣል

አጠቃላይ በሆነ መልኩ በኣል የማኅበረሰቡ ሰዎች በአንድነት የሚያከብሩት ሁኔታ ነው።

  • በብሉይ ኪዳን መሠረት፣ “በዓል” ቃል በቃል፣ “የተወሰነ ወይም የተመደበ ቀን” ማለት ነው።
  • እስራኤላውያን የሚያከብሯቸው በዓሎች እግዚአብሔር እንዲጠብቁት ባዘዛቸው መሠረት በተለየ ሁኔታ የተመደበ ጊዜ ወይም ወቅት ናቸው።
  • እስራኤላውያን በየዓመቱ የሚያከብሯቸው ዋና ዋና በዓሎች አሉ፤
  • የፋሲካ በዓል
  • የቂጣ በዓል
  • የመከር በዓል
  • በዓለ-ሃምሳ
  • የመለከት በዓል
  • የስርየት በዓል
  • የዳስ በዓል
  • የእነዚህ በዓሎች ዓላማ እግዚአብሔርን ለማመስገንና ሕዝቡን ለመታደግ፣ ለመጠበቅና የሚያስፈልገውን በመስጠት ያደረጋቸውን ድንቅ ነገሮች ለማስታወስ ነው።