am_tw/bible/other/falsewitness.md

840 B

የሐሰት ምስክር፣ ጠማማ ምስክር፣ ሐሰተኛ ወሬ

“ሐሰተኛ ምስክር” እና “ጠማማ ምስክር” ሰዎችን ወይም ሁኔታዎችን በተመለከተ እውነቱን የማይናገር ሰው ሲሆን፣ ብዙውን ጊዜ እንዲህ ሲደረግ የሚታየው በመደበኛ ፍርድ ቦታ ነው።

  • ሐሰተኛ ወሬ የሚባለው ሐሰተኛ ምስክር የተናገረው ነው።
  • “በሐሰት መመስከር” ሰዎችን ወይ ሁኔታዎችን በተመለከተ እውነት ያልሆነውን መናገር ነው።
  • አንድ ሰው እንዲቀጣ ወይም እንዲገደል ለማድረግ ሰዎች ሐሰተኛ ምስክሮችን ቀጥረው ስለነበረበት ሁኔታ መጽሐፍ ቅዱስ በርካታ ታሪኮች አሉት።