am_tw/bible/other/divorce.md

626 B

መፋታት፣ ፍቺ

መፋታት ጋብቻ የሚቋረጥበት ሕጋዊ አሠራር ነው። ፍቺ ያደረጉ ባልና ሚስት ከእንግዲህ ትዳር ውስጥ አይደሉም ማለት ነው።

  • የመፋታት ቃል በቃል ትርጕሙ፣ “መለያየት” ወይም፣ “ማሰናበት” ማለት ሲሆን፣ ሌሎች ቋንቋዎችም እንዲህ ያሉ ፈሊጣዊ አነጋገሮች ይኖሩዋቸዋል።
  • “የፍቺ ጽሑፍ” የሚለው፣ “ባልና ሚስቱ መለያየታቸውን የሚያመለክት ሰነድ” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል።