am_tw/bible/other/desert.md

847 B

በረሐ፣ ምድረ በዳ

በረሐ ወይም ምድረ በዳ በጣም ጥቂት ተክሎችና ዛፎች ብቻ የሚያድጉበት ደረቅና ጠፍ ቦታ ነው።

  • በረሐ ጥቂት ተክሎች ወይም እንስሳት ያሉት ደረቅ የአየር ፀባይ ያለው አካባቢ ነው።
  • እንዲህ ያለው ቦታ በጣም አስቸጋሪ በመሆኑ በረሐ ውስጥ የሚኖሩ በጣም ጥቂት ሰዎች ናቸው። ይህ ቦታ፣ “ምድረ በዳ” ተብሎም ይጠራል።
  • “ምድረ በዳ” ሲባል በጣም ሩቅ፣ የተተወና ከሰዎች መኖሪያ የተገለለ የሚል ዐሳብ አለው።
  • ይህ ቃል፣ “ሰው የማይኖርበት” ወይም፣ “ሩቅ ቦታ” ወይም “የተተወ ቦታ” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል።