1.1 KiB
1.1 KiB
መጋረጃ
መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን “መጋረጃ” የሚያመለክተው መገናኛው ድንኳንንና ቤተ መቅደሱን ለመሥራት ጥቅም ላይ ይውል የነበረውን ወፍራምና በጣም ከባድ ጨርቅ ነበር።
- መገናኛው ድንኳን የተሠራው ከላይና ከጎን በተዘረጉ አራት ተደራራቢ መጋረጃዎች ነበር። እነዚህ መጋረጃዎች ከጨርቅ ወይም ከእንስሳት ቆዳ ይሠሩ ነበር።
- የጨርቅ መጋረጃዎች በመገናኛው ድንኳን አደባባይ ዙሪያ ግድግዳ በመሆን ያገለግሉ ነበር። እነዚህ መጋረጃዎች ከተልባ እግር ማለትም ከናይለንም ይሠሩ ነበር።
- በመገናኛው ድንኳንም ሆነ በቤተ መቅደሱ ግንባታ ሥራ በቅድስተ ቅዱሳኑና በተቀደሰው ቦታ መካከል በጣም ትልቅ የጨርቅ መጋረጃ ይደረግ ነበር። ኢየሱስ መስቀል ላይ በሞተ ጊዜ በተአምር ለሁለት የተቀደደው ይኸው መጋረጃ ነበር።