am_tw/bible/other/confirm.md

1.4 KiB

ማጽናት፣ ማረጋገጥ፣ ማጽኛ

“ማጽናት” የሚለው ቃል አንድ ነገር እውነት ወይም እርግጥ ወይም አስተማማኝ መሆኑን መናገር ወይም መመልከት ማለት ነው።

  • ብሉይ ኪዳን ውስጥ ከእነርሱ ጋር የገባውን ኪዳን እንደሚያጸና እግዚአብሔር ለሕዝቡ ይናገራል። ይህም ማለት ለእነርሱ የገባውን ቃል እንደሚጠብቅና እንደሚፈጽም መናገሩ ነው።
  • አንድ ሰው የጻፈውን ማጽናት እርሱ የጻፈው እውነት መሆኑን መቀበል ማለት ነው።
  • የእምነት “ማጽኛ” እውነት መሆኑን በሚያረጋግጥ መልኩ ለሰዎች የኢየሱስ ክርስቶስን ወንጌል ማስተማር ማለት ነው።
  • “በመሐላ ማጽናት” አንድ ነገር እውነተኛ አስተማማኝ መሆኑን ጠንከር አድርጎ መናገር ወይም መማል ማለት ነው።
  • ማጽናት የሚለውን የመተርጎም፣ “እውነት መሆኑን መናገር” ወይም፣ “አስተማማኝነቱን መግለጥ” ወይም፣ “ከዚያ ጋር መስማማት” ማለት ይቻላል። በዐውዱ መሠረትም፣ “ማረጋገጥ” ወይም፣ “ቃልን መስጠት” ማለት ይቻላል።