am_tw/bible/other/cedar.md

658 B

ዝግባ

“ዝግባ” የሚለው ቃል ቀይ ቡናማ እንጨት ያለው ሾጣጣ ጫፍ ያለውን ግዙፍ ዛፍ ያመለክታል። እንደ ሌሎች ሾጣጣ ዛፎች ሁሉ እንደ መርፌ የሾሉ ቅጠሎች አሉት።

  • ብሉይ ኪዳን ይህ ዛፍ በብዛት ይበቅልበት ከነበረው ከሊባኖስ ጋር አያይዞ ስለ ዝግባ ዛፍ ብዙ ይናገራል።
  • የዝግባ ዛፍ የኢየሩሳሌም ቤተ መቅደስ ሲሠራ ጥቅም ላይ ውሏል።
  • መሥዋዕት ለማቅረብና ሰዎችን በማንጻት ሥርዓትም ጥቅም ላይ ይውል ነበር።