am_tw/bible/other/burntoffering.md

936 B

የሚቃጠል መሥዋዕት፣ በእሳት መሠዋት

“የሚቃጠል መሥዋዕት” የሚባለው መሠዊያው ላይ በእሳት ተቃጥሎ ለእግዚአብሔር የሚቀርብ መሥዋዕት ዐይነት ነው። የሚቃጠለው ለሕዝቡ ኀጢአት ስርየት ለመሆን ነው። “በእሳት መሠዋት” ተብሎም ይጠራል።

  • ለዚህ መሥዋዕት የሚቀርብ እንስሳት ብዙውን ጊዜ በጎችና ፍየሎች ቢሆኑም፣ በሬዎችና ወፎችም መሥዋዕት ይሆናሉ።
  • የሚቃጠል መሥዋዕት በሚቀርብበት ጊዜ ከቆዳው ውጪ የእንስሳው አካል በሙሉ ይቃጠላል። ቆዳው ወይም ሌጦው ለካህኑ ይሰጠዋል።
  • በዓመት ሁለት ጊዜ የሚቃጠል መሥዋዕት እንዲያቀርቡ እግዚአብሔር የአይሁድን ሕዝብ አዝዞ ነበር።