am_tw/bible/other/blemish.md

1.0 KiB

እንከን፣ ነውር

“እንከን” ወይም ነውር አንድ እንስሳ ወይም ሰው ላይ ያለ ጉድለትን ወይም ሙሉ ያለመሆንን ያመለክታል። ሰዎች ላይ ያለ በደልን ወይም መንፈሳዊ ጉድለትንም ያመለክታል።

  • አንዳንድ መሥዋዕቶችን በተመለከተ እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን ሲናገር እንከን ወይም ነውር የሌለበትን እንስሳ እንዲያቀርቡ መመሪያ ሰጥቷል።
  • ይህ ሥዕል ኢየሱስ ክርስቶስ ምንም ኃጢአት የሌለው ፍጹም መሥዋዕት መሆኑን ያመለክታል።
  • በክርስቶስ የሚያምኑ አማኞች በእርሱ ደም ከኃጢአታቸው ነጸተዋል፤ ስለዚህም እንከን ወይም ነውር የሌለባቸው ተብለዋል።
  • እንደ ዐውደ ምንባቡ ይህን፣ “ጉድለት” ወይም፣ “ነቀፋ” ወይም፣ “ኃጢአት” በማለት መተርጎም ይቻላል።