am_tw/bible/other/acquit.md

690 B

ነጻ ማድረግ

“ነጻ ማድረግ” አንድ ሰው ከተከሰሰበት በደል ወይም ርኩሰት ነጻ መሆኑን በግልጽ መናገር ወይም ማወጅ ማለት ነው።

  • መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ኃጢአተኛን ይቅር ማለትን አስመልክቶ ለመናገር ይህ ቃል ጥቅም ላይ ይውላል።
  • ብዙውን ግዜ ዐውዱ በእግዚአብሔር ላይ ኃጢአት ያደረጉና በእርሱ ላይ ያመፁ ሰዎችን አለ አግባብ ነጻ ማድረግን ይመለከታል።
  • “ንጽህናን ማወጅ”ወይም “ከበደል ነጻ ማድረግ” ተብሎ መተርጎም ይችላል