am_tw/bible/names/zechariahnt.md

681 B

ዘካርያስ - (አዲስ ኪዳን)

ዘካርያስ በኋላ መጥምቁ ዮሐንስን የወለደ የአይሁድ ካህን ነበር።

  • ዘካርያስ እግዚአብሔርን ይወድና ለእርሱም ይታዘዝ ነበር።
  • ዘካርያስና ሚስቱ ኤልሳቤጥ ልጅ እንዲወልዱ አጥብቀው ብዙ ዓመት ቢጸልዩም፣ መውለድ አልቻሉም ነበር። በጣም ባረጁ ጊዜ ግን እግዚአብሔር ጸሎታቸውን ሰምቶ ልጅ ሰጣቸው።
  • የእርሱ ልጅ ዮሐንስ የመሲሑን መንገድ የሚያዘጋጅ ነቢይ እንደሚሆን ዘካርያስ ትንቢት ተናገረ።