ሳዶቅ
ሳዶቅ በንጉሥ ዳዊት ዘመን በእስራኤል የነበረ ሁነኛ ሊቀ ካህን ነበር።
- አቤሴሎም ባመፀበት ጊዜ ሳዶቅ ዳዊትን ደግፎ ነበር፤ የቃል ኪዳኑን ታቦት ወደ ኢየሩሳሌም እንዲያመጣ ዳዊትን የረዳው እርሱ ነበር።
- ከዓመታት በኋላ የዳዊት ልጅ ሰሎሞን ንጉሥ እንዲሆን ሲቀባ ሥነ ሥርዓቱ ላይ ተገኝቶ ነበር።
- በነህምያ ዘመን የኢየሩሳሌም ቅጥር ሲሠራ ሳዶቅ የተባሉ ሁለት ሰዎች ረድተው ነበር።
- የንጉሥ ኢዮአታም አያት ስም ሳዶቅ ይባል ነበር።