am_tw/bible/names/zadok.md

713 B

ሳዶቅ

ሳዶቅ በንጉሥ ዳዊት ዘመን በእስራኤል የነበረ ሁነኛ ሊቀ ካህን ነበር።

  • አቤሴሎም ባመፀበት ጊዜ ሳዶቅ ዳዊትን ደግፎ ነበር፤ የቃል ኪዳኑን ታቦት ወደ ኢየሩሳሌም እንዲያመጣ ዳዊትን የረዳው እርሱ ነበር።
  • ከዓመታት በኋላ የዳዊት ልጅ ሰሎሞን ንጉሥ እንዲሆን ሲቀባ ሥነ ሥርዓቱ ላይ ተገኝቶ ነበር።
  • በነህምያ ዘመን የኢየሩሳሌም ቅጥር ሲሠራ ሳዶቅ የተባሉ ሁለት ሰዎች ረድተው ነበር።
  • የንጉሥ ኢዮአታም አያት ስም ሳዶቅ ይባል ነበር።