am_tw/bible/names/succoth.md

1.0 KiB

ሱኮት

ብሉይ ኪዳን ውስጥ ሱኮት ተብለው የተጠሩ ሁለት ከተሞች አሉ። ሱኮት “መጠለያ” ወይም፣ “መጠጊያ” ማለት ነው

  • ሱኮት ተብላ የተጠራችው የመጀመሪያዋ ከተማ ከዮርዳኖስ ወንዝ ምሥራቅ ትገኝ ነበር
  • ያዕቆብ ከቤተ ሰቡ እና ከነበሩት የቤት እንስሳት ጋር በሱኮት ቆዩ፤ በዚያም መጠጊያ መጠለያ ሠራላቸው
  • ከመቶ ዓመታት በኋላ ጌዴዎንና ተዳክመው የነበሩት አብረውት ያሉ ሰዎች ምድያማውያንን እያሳደዱ በነበረ ጊዜ በሱኮት ቆይታ አድርገው ነበር፤ እዚያ የነበሩ ሰዎች ግን ምግብ እንኳ ሊሰጧቸው አልፈለጉም
  • ሁለተኛዋ ሱኮት የምትገኘው በሰሜናዊ የግብፅ ድንበር ሲሆን ከግብፅ ባርነት አምልጠው ቀይ ባሕርን ከተሻገሩ በኋላ ካረፉባቸው ቦታዎች አንዷ ነበረች