am_tw/bible/names/samson.md

970 B

ሳምሶን

ሳምሶን ከእስራኤል መሳፍንት ወይም ታዳጊ አንዱ ነበር። ሳምሶን ከዳን ነገድ ነበር።

  • እግዚአብሔር ለሳምሶን የእስራኤልን ጠላቶች ማለት ፍልስጥኤማውያንን የሚያጠቃበት አስደናቂ ልዕለ ሰብ ብርታት ሰጥቶት ነበር
  • ሳምሶን ጠጉሩን ላለመቆረጥና አልኮል ወይም ሌላ የሚያሰክር ነገር ላለመጠጣት ስለት ነበረበት
  • አታላይ ሚስቱ ደሊላ ላቀረበችለት ልመና በመታለል የብርታቱን ምስጢር በመናገሩ ብርታቱን እንዲያጣ ጠጉሩን ቆረጠችው
  • ሳምሶን እስር ላይ እያለ እግዚአብሔር ብርታቱን መልሶ እንዲገኝና ከብዙ ፍልስጥኤማውያን ጋር የሐሰተኛው አምላክ የዳጎንን ቤተመቅደስ ማፍረስ እንዲችል አደረገ