am_tw/bible/names/rome.md

780 B

ሮም፣ ሮማዊ

በዚህ ባለንበት ዘመን ሮም የኢጣልያ ዋና ከተማ ናት።

  • ኢየሱስና ሐዋርያቱ ባገለገሉበት ዘመን ሮም የሮም መንግሥት ማዕከል ነበረች።
  • የሮም መንግሥት እስራኤልን ጨምሮ ሜዲትራንያን ባሕር ዙሪያ የነበረውን አካባቢ ሁሉ ይገዛ ነበር።
  • “ሮማዊ” የሚለው ቃል ሮማውያን ዜጎችንና ባለ ሥልጣኖችን ጨምሮ የሮም መንግሥት ከሚገዛው አካባቢ ጋር የተያያዙ ነገሮችን ሁሉ ያመለክታል።
  • ሐዋርያው ጳውሎስ የኢየሱስን የምሥራች በመስበኩ እስረኛ ሆኖ ወደ ሮም ከተማ ተወስዶ ነበር።