am_tw/bible/names/priscilla.md

860 B

ጵርስቅላ

ጵርስቅላ ከባልዋ ከአቂላ ጋር በሐዋርያዊ ተልዕኮው ከሐዋርያው ጳውሎስ ጋር አብራ ትሠራ የነበረች የመጀመሪያው መቶኛ ዓመት አይሁዳዊት ክርስቲያን ነበረች።

  • ጳውሎስ አቂላና ጵርስቅላን ያገኘው በቆሮንቶስ ነበር።
  • አቂላና ጵርስቅላ ለጊዜው በሮም ኖረዋል።
  • ባልና ሚስቱ ከጳውሎስ ጋር ድንኳን ይሰፉ ነበር፤ በሐዋርያዊ ሥራውም ይረዱት ነበር።
  • አቂላና ጵርስቅላ የጳውሎስ ረዳቶች መሆናቸው አዲስ ኪዳን ውስጥ ብዙ ጊዜ ተጠቅሷል።
  • ጵርስቅላ በጥንት ቤተ ክርስቲያን የነበረች ሴት መምህር መሆንዋ እንደ ምሳሌ ይጠቀሳል።