860 B
860 B
ጵርስቅላ
ጵርስቅላ ከባልዋ ከአቂላ ጋር በሐዋርያዊ ተልዕኮው ከሐዋርያው ጳውሎስ ጋር አብራ ትሠራ የነበረች የመጀመሪያው መቶኛ ዓመት አይሁዳዊት ክርስቲያን ነበረች።
- ጳውሎስ አቂላና ጵርስቅላን ያገኘው በቆሮንቶስ ነበር።
- አቂላና ጵርስቅላ ለጊዜው በሮም ኖረዋል።
- ባልና ሚስቱ ከጳውሎስ ጋር ድንኳን ይሰፉ ነበር፤ በሐዋርያዊ ሥራውም ይረዱት ነበር።
- አቂላና ጵርስቅላ የጳውሎስ ረዳቶች መሆናቸው አዲስ ኪዳን ውስጥ ብዙ ጊዜ ተጠቅሷል።
- ጵርስቅላ በጥንት ቤተ ክርስቲያን የነበረች ሴት መምህር መሆንዋ እንደ ምሳሌ ይጠቀሳል።