am_tw/bible/names/phinehas.md

1.0 KiB

ፊንሐስ

ብሉይ ኪዳን ውስጥ ፊንሐስ ተብለው የተጠሩ ሁለት ሰዎች አሉ።

  • አንዱ ፊንሐስ የአሮን የልጅ ልጅና በእስራኤል ሐሰተኛ አማልክት መመለክን አጥብቆ ይቃወም የነበረው ካህን ነበር።
  • ምድያማውያን ሴቶች ጋር በመጋባታቸውና ሐሰተኛ አማልክቶቻቸውንም በማምለካቸው እነርሱን ለመቅጣት ያህዌ ከላከው መቅሠፍት እስራኤልን ያዳነ ፊንሐስ ነበር።
  • በተለያየ ጊዜ ፊንሐስ ምድያማውያንን ለማጥፋት ከእስራኤል ሰራዊት ጋር ሄዷል።
  • ፊንሐስ ተብሎ የተጠራው ሌላው ሰው በነቢዩ ሳሙኤል ዘመን ከነበረው ካህኑ ዔሊ ክፉ ልጆች አንድ ነበር።
  • ፍልስጥኤማውያን እስራኤልን በጠቁበትና የኪዳኑ ታቦትንም በወሰዱበት ጊዜ ፊንሐስና ወንድሙ ሐፍኒ ተገድለዋል።