am_tw/bible/names/nebuchadnezzar.md

663 B

ናቡከደነፆር

ናቡከደነፆር የባቢሎን መንግሥት ንጉሥ ነበር። የእስራኤልና የይሁዳ መንግሥታት በነበሩበት ዘመን ባቢሎን ገናና መንግጥ ነበረች።

  • ናቡከደነፆር ብዙ ሕዝቦችን ድል ያደረገ በጣም ብርቱ ሰራዊት ነበረው።
  • በናቡከደነፆር አመራር ዘመን የባቢሎን ሰራዊት የይሁዳን መንግሥት ድል በማድረግ አብዛኛውን ሕዝብ በምርኮኝነት ወደ ባቢሎን ወስዶ ነበር። ይህ “የባቢሎን ምርኮ” ዘመን ለ70 ዓመት ዘልቋል።