1.0 KiB
1.0 KiB
ሊባኖስ
ሊባኖስ ከእስራኤል በስተ ሰሜን ሜዲትራንያን ባሕር ዳርቻ የምትገኝ በጣም የምታምር ተራራማ ቦታ ናት። መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን ይህ አካባቢ ጥቅጥቅ ባሉት ደኖቹም ይታወቅ ነበር።
- የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ መሥሪያ የሚሆን ዝግባ እንጨት እንዲያመጡለት ንጉሥ ሰሎሞን ወደ ሊባኖስ ሠራተኞች ልኮ ነበር።
- የሊባኖስ ጥንታዊ ኗሪዎች ሊንቃውያን የተሰኙት ሕዝብ ሲሆኑ በንግዱ እንቅስቃሴ በከፍተኛ ደረጃ ጥቅም ላይ የዋሉ መርከቦችን የመሥራት ችሎታ ነበራቸው።
- የጢሮስና የሲዶና ከተሞች ሊባኖስ ውስጥ ነበር። ውድ ዋጋ ያለው ሐምራዊ ቀለም ያለ የተነከረ ጨርቅ ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለው በእነዚህ ከተሞች ነበር።