am_tw/bible/names/lebanon.md

1.0 KiB

ሊባኖስ

ሊባኖስ ከእስራኤል በስተ ሰሜን ሜዲትራንያን ባሕር ዳርቻ የምትገኝ በጣም የምታምር ተራራማ ቦታ ናት። መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን ይህ አካባቢ ጥቅጥቅ ባሉት ደኖቹም ይታወቅ ነበር።

  • የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ መሥሪያ የሚሆን ዝግባ እንጨት እንዲያመጡለት ንጉሥ ሰሎሞን ወደ ሊባኖስ ሠራተኞች ልኮ ነበር።
  • የሊባኖስ ጥንታዊ ኗሪዎች ሊንቃውያን የተሰኙት ሕዝብ ሲሆኑ በንግዱ እንቅስቃሴ በከፍተኛ ደረጃ ጥቅም ላይ የዋሉ መርከቦችን የመሥራት ችሎታ ነበራቸው።
  • የጢሮስና የሲዶና ከተሞች ሊባኖስ ውስጥ ነበር። ውድ ዋጋ ያለው ሐምራዊ ቀለም ያለ የተነከረ ጨርቅ ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለው በእነዚህ ከተሞች ነበር።