am_tw/bible/names/josephot.md

766 B

ዮሴፍ (ብሉይ ኪዳን)

ዮሴፍ የያዕቆብ አሥራ አንደኛ ልጅ ሲሆን፣ ለራሔል ደግሞ የመጀመሪያ ልጇ ነበር።

  • ዮሴፍ በአባቱ ዘንድ በጣም የተወደደ ልጅ ስለነበር ወንድሞቹ ቀኑበት፤ ለባርነትም ሸጡት።
  • በግብፅ አገር ባርያና እስረኛ መሆንን ጨምሮ ዮሴፍ በአስቸጋሪ ጊዜ ውስጥ አልፏል፤ ያም ሆኖ ግን ለእግዚአብሔር ታማኝነቱን ጠብቋል።
  • እግዚአብሔር ግብፅ ውስጥ ሁለተኛ ወደነበረው የሥልጣን ደረጃ አደረሰው፤ ግብፅንና የአባቱን ቤተሰቦች በራብ ከመሞት እንዲያድን ተጠቀመበት።