am_tw/bible/names/johnmark.md

774 B

ዮሐንስ (ማርቆስ)

ዮሐንስ ማርቆስ በሐዋርያዊ ተልዕኮው ከሐዋርያው ጳውሎስ ጋር ከተጓዙ ሰዎች አንዱ ሲሆን፣ ማርቆስ ተብሎ ይጠራል።

  • ዮሐንስ ማርቆስ በመጀመሪያው ሐዋርያዊ ተልዕኳቸው ከበርናባስና ከጳውሎስ ጋር አብሮ ተጉዞ ነበር።
  • ጴጥሮስ በኢየሩሳሌም በታሰረ ጊዜ አማኞች ለእርሱ እየጸለዩ የነበረው የዮሐንስ ማርቆስ እናት ቤት ውስጥ ነበር።
  • ማርቆስ ከመጀመሪያዎቹ ሐዋርያት አንዱ ባይሆንም ከሐዋርያው ጳውሎስና ጴጥሮስ ተምሯል፤ በአገልግሎትም ከእነርሱ ጋር ሠርቷል።