am_tw/bible/names/hittite.md

1.1 KiB

ኬጢያዊ

ኬጢያውያን በልጁ በከነዓን በኩል የካም ዘሮች ነበር። በአሁኑ ዘመን ቱርክ በሚባለውና ከፐስቲና በስተ ሰሜን ባለው አካባቢ ታላቅ መንግሥት ሆነው ነበር።

  • በሥጋዊም ሆነ በመንፈሳዊ ደረጃ ኬጢያውያን ሁሌም ለእስራኤል ስጋት ነበሩ።
  • የሞተችው ሚስቱ ሣራን እዚያ በነበረ ዋሻ ውስጥ መቅበር እንዲችል አብርሃም ከኬቲያዊው ኤፍሮን ርስት ገዛ። የኋላ ኋላ አብርሃምና ከዘሮቹ ብዙዎቹ የተቀበሩት በዚያ ዋሻ ነበር።
  • ሁለት ኬቲያውያን ሴቶች ባገባ ጊዜ የኤሳው ወላጆች አዝነው ነበር።
  • ከዳዊት ኀያላን ሰዎች አንዱ ኬጢያዊው ኦርዮን ነበር።
  • ከሰሎሞን ባዕዳን ሚስቶች አንዳንዶቹ ኬጢያውያን ነበር። እነርሱ ያመልኳቸው ከነበሩ ሐሰተኛ አማልክት የተነሣ እነዚህ ሴቶች የሰሎሞንን ልብ እግዚአብሔርን ከማምለክ መለሱት።