am_tw/bible/names/hannah.md

784 B

ሐና

ሐና ብሉይ ኪዳኑ ውስጥ የነቢዩ ሳሙኤል እናት ናት። ከሕልቃና ሚስቶች አንዷ ነበረች።

  • ሐና ልጅ መውለድ አለመቻልዋ ከባድ ሐዘን ሆኖባት ነበር።
  • ሐና እግዚአብሔር ወንድ ልጅ አንዲሰጣት ቤተ መቅደስ ውስጥ አጥብቃ ጸለየች፣ ያ ልጅ ለእግዚአብሔር አገልግሎት እንደሚለይም ቃል ገባች።
  • እግዚአብሔር የለመነችውን ሰጣት፤ ሕፃኑ ሳሙኤል ካደገ በኋላ በካህኑ በዔሊ መሪነት ሥር ቤተ መቅደስ ውስጥ እንዲያገለግል አመጣችው።
  • ከዚያ በኋላ እግዚአብሔር ለሐና ሌሎች ልጆችንም ሰጥቷታል።