am_tw/bible/names/hananiah.md

1.2 KiB

አናንያ

ከትንቢተ ዳንኤል እንደምንመለከተው አናንያ በምርኮ ዘመን ወደ ባቢሎን ተወስደው ስለነበሩ አስተዋይ አይሁዳውያን ወጣቶች አንዱ ነበር። ይበልጥ የሚታወቀው ሲድራቅ በተሰኘው ስሙ ነው።

  • ባሳየው የፀባይ ብልጫና እግዚአብሔር ከሰጠው ችሎታ የተነሣ ባቢሎናውያን ለአናንያ ከፍተኛ ሥልጣን ሰጥተውት ነበር።
  • የባቢሎን ንጉሥ ለአናንያ ሲድራቅ የሚል ስም ሰጠው።
  • ለንጉሡ መስገድ ባለ መፈለጋቸው ከሌሎች አይሁዳውያን ጓደኞቹ ጋር ሲድራቅ እሳት ውስጥ ተጥሎ ነበር። እነርሱ ላይ ምንም ጉዳት እንዳይደርስ በማድረግ እግዚአብሔር ኀይሉን አሳየ።
  • በተለያዩ የብሉይ ኪዳን ክፍሎች እናንያ (ሐናንያ) የሚባሉ ይህን ያህል ታዋቂነት ያልነበራቸው ሰዎች ነበሩ።
  • አንደኛው አናንያ (ሐናንያ) በነቢዩ ኤርምያስ ዘመን የነበረው ሐሰተኛ ነቢይ ነው።