am_tw/bible/names/gaza.md

1.1 KiB

ጋዛ

መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን ጋዛ የሜዲትራንያን ባሕር ዳርቻ አካባቢ፣ ከኢየሩሳሌም ደቡብ ምዕራብ 77 ኪሎ ሜትር፣ ከአሽዶድ በስተ ሰሜን 38 ኪሎ ሜትር ላይ ትገኝ የነበረች በጣም አስፈላጊ የፍልስጥኤማውያን ከተማ ነበረች።

  • በጥንት ዘመን ጋዛ በእስያና በግብፅ መሐል ያለች የወታደራዊና የንግድ መተላለፊያ በር ነበረች።
  • በዚህ ዘመንም ጋዛ ጋዛ ሰርጥ ውስጥ በጣም አስፈላጊ ወደብ ስትሆን፣ ሜዴትራንያን ባሕር ዳርቻ አካባቢ የምትገኝና በስተ ሰሜንና በስተ ምሥራቅ ከእስራኤል ጋር፣ በስተ ደቡብ ከግብፅ ጋር ትዋሰናለች።
  • ፍልስጥኤማውያን ሳምሶንን ከያዙት በኋላ የወሰዱት ወደ ጋዛ ነበር።
  • ወንጌላዊው ፊልጶስ ኢትዮጵያዊውን ጃንደረባ ያገኘው ወደ ጋዛ በሚወስደው የበረሐ መንገድ ላይ ነበር።