am_tw/bible/names/gath.md

871 B

ጌት

ጌት ከአምስቱ የፍልስጥኤም ዋና ዋና ከተሞች አንዷ ነበረች። የምትገኘው ከአቃሮን በስተ ሰሜንና ከአሾዶድና ከአስቄሎና በስተ ምሥራቅ ነበር።

  • የፍልስጥኤማውያን ጀግና ጎልያድ አገር ጌት ነበር።
  • በሳሙኤል ዘመን ፍልስጥኤማውያን የቃል ኪዳኑን ታቦት ከእስራኤል ዘርፈው አአሽደድ ወደ ነበረው የአረማውያን ቤተ መቅደስ ከዚያም ወደ ጌት ወስደውት ነበር። ሆኖም. እግዚአብሔር የነዚህ ከተሞችን ሰዎች በበሽታ በመቅጣቱ፣ ወደ እስራኤል መለሱት።
  • ዳዊት ከንጉሥ ሳኦል በሸሸ ጊዜ ወደ ጌት ሄዶ ከሁለት ሚስቶቹ ጋር ለአጭር ጊዜ እዚያ ኖረ።