am_tw/bible/names/euphrates.md

1.0 KiB

ኤፍራጥስ

ኤፍራጥስ በኤደን የአትክልት ቦታ ውስጥ ያልፉ ከነበሩ አራት ወንዞች አንዱ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በተደጋጋሚ የተጠቀሰ ወንዝ ነው፣ አንዳንዴ፣ “ወንዙ” በመባል በአጭር ቃል ተጠርቷል።

  • በዚህ ዘመን ኤፍራጥስ ተብሎ የሚጠራው ወንዝ የሚገኘው መካከለኛው ምሥራቅ ውስጥ ሲሆን፣ በእስያ ካሉት ወንዞች ረጅሙና በጣም ጠቃሚው ወንዝ ነው።
  • ከጤግሮስ ወንዝ ጋር በአንድነት ኤፍራጥስ ሜስፖታሚያ በመባል ከሚታወቀው ምድር ጋር ይዋሰናል።
  • አብርሃም የተገኘባት የጥንቷ ዑር ከተማ የምትገኘው የኤፍራጥስ ወንዝ ልሳን ላይ ነበር።
  • ይህ ወንዝ ለአብርሃም እንደሚሰጠው እግዚአብሔር ቃል የገባለት ምድር ድንበሮች አንዱ ነው። (ዘፍጥረት 15፣18)