am_tw/bible/names/ethiopia.md

1.3 KiB

ኢትዮጵያ፣ ኢትዮጵያዊ

ኢትዮጵያ ከግብፅ በስተደቡብ ያለች አፍሪካዊት አገር ስትሆን፣ በስተምዕራብ የአባይ ወንዝ፣ በስተምሥራቅ ደግሞ ከቀይ ባሕር ጋር ትዋሰናለች። ከኢትዮጵያ ምድር የተገኘ ሰው ኢትዮጵያዊ ይባላል።

  • የጥንቷ ኢትዮጵያ ከግብፅ በስተደቡብ ያለች ሱዳንን፣ የአሁኗ ኢትዮጵያን፣ ሶማልያን፣ ኬንያን፣ ዩጋንዳን፣ ማዕከላዊ ሪፖብሊክንና ቻድን የመሳሰሉ በርካታ የዘመኑ አፍሪካ አገሮችን የምታካትት ነበረች።
  • መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ኢትዮጵያ አንዳንዴ “ኩሽ” ወይም፣ “ኑቢያ” ትባላለች።
  • የኢትዮጵያ አገሮች (“ኩሽ”) እና ግብፅ ብዙ ጊዜ በአንድነት መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ተጠቅሷል፤ እንዲህ የሆነው ጎረቤታሞች ስለሆኑና ሕዝቦቻቸው ተመሳሳይ ጥንተአባቶች ስለነበሯቸው ሊሆን ይችላል።
  • እግዚአብሔር ፊልጶስን ወደምድረ በዳ ላከው፣ እርሱም የኢየሱስ ክርስቶስን ምሥራች ለኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ተናገረ።