am_tw/bible/names/esther.md

1.2 KiB

አስቴር

አይሁድ በባቢሎን በምርኮ በነበሩበት ዘመን የፋርስ መንግሥት ልዕልት የሆነች አይሁዳዊት ሴት ናት።

  • አስቴር የፋርስ ንጉሥ የአርጤክስስ ልዕልት መሆን እንዴት እንደቻለችና ሕዝቧን ለማዳን እግዚአብሔር እንደተጠቀመባት መጽሐፈ አስቴር ይናገራል።
  • አስቴር አባትና እናት ያልነበራት ስትሆን፣ ያሳደጋት እግዚአብሔርን የሚፈራው ሽማግሌው አጎቷ መርዶክዮስ ነበር።
  • ለአሳዳጊ አባቷ ታዛዥ መሆንዋ፣ ለእግዚአብሔርም ታዛዥ እንድትሆን ረዳት።
  • ሕዝቧ አይሁድን ለማዳን ስትል ሕይወቷን ለአደጋ በማጋለጥ አስቴር ለእግዚአብሔር ታዝዛለች።
  • መጽሐፈ አስቴር በታሪክ ውስጥ የሚፈጸሙ ነገሮችን ለመቆጣጠር የእግዚአብሔርን ሉዓላዊነትና በተለይም እንዴት ሕዝቡን እንደሚጠብቅና ለእርሱ በሚታዘዙ ሰዎች በኩል እንዴት እንደሚሠራ ይገልጻል።