10 lines
1.2 KiB
Markdown
10 lines
1.2 KiB
Markdown
|
# አስቴር
|
||
|
|
||
|
አይሁድ በባቢሎን በምርኮ በነበሩበት ዘመን የፋርስ መንግሥት ልዕልት የሆነች አይሁዳዊት ሴት ናት።
|
||
|
|
||
|
* አስቴር የፋርስ ንጉሥ የአርጤክስስ ልዕልት መሆን እንዴት እንደቻለችና ሕዝቧን ለማዳን እግዚአብሔር እንደተጠቀመባት መጽሐፈ አስቴር ይናገራል።
|
||
|
* አስቴር አባትና እናት ያልነበራት ስትሆን፣ ያሳደጋት እግዚአብሔርን የሚፈራው ሽማግሌው አጎቷ መርዶክዮስ ነበር።
|
||
|
* ለአሳዳጊ አባቷ ታዛዥ መሆንዋ፣ ለእግዚአብሔርም ታዛዥ እንድትሆን ረዳት።
|
||
|
* ሕዝቧ አይሁድን ለማዳን ስትል ሕይወቷን ለአደጋ በማጋለጥ አስቴር ለእግዚአብሔር ታዝዛለች።
|
||
|
* መጽሐፈ አስቴር በታሪክ ውስጥ የሚፈጸሙ ነገሮችን ለመቆጣጠር የእግዚአብሔርን ሉዓላዊነትና በተለይም እንዴት ሕዝቡን እንደሚጠብቅና ለእርሱ በሚታዘዙ ሰዎች በኩል እንዴት እንደሚሠራ ይገልጻል።
|