am_tw/bible/names/david.md

1.1 KiB

ዳዊት

ዳዊት እግዚአብሔርን በመውደዱና እርሱን በማገልገሉ የታወቀ ሁለተኛው የእስራኤል ንጉሥ ነው። የመዝሙራት መጽሐፍ ዋናው ጸሐፊም እርሱ ነው።

  • ዳዊት ገና ትንሽ ልጅ እያለ የቤተ ሰቡን በጎች ሲጠብቅ ሁለተኛው የእስራኤል ንጉሥ እንዲሆን እግዚአብሔር መረጠው።
  • ዳዊት ብርቱ ጦረኛ ሆነ፤ በጠላቶቻቸው ላይ እንዲዘምቱ የእስራኤልን ሰራዊት መርቷል። ፍልስጥኤማዊው ጎልያድን ማሸነፉ በጣም ታዋቂ እንዲሆን አድርጎታል።
  • ንጉሥ ሳኦል ዳዊትን ለመግደል ሞክሮ ነበር፤ እግዚአብሔር ግን እርስን ጠብቀው፤ ከሳኦል ሞት በኋላም ንጉሥ አደረገው።
  • ዳዊት በጣም ከባድ ኀጢአት ፈጽሞ ነበር፤ ይሁን እንጂ ንስሐ አደረገ፤ እግዚአብሔርም ይቅር አለው።
  • የንጉሥ ዳዊት ዘር በመሆኑ መሲሑ ኢየሱስ፣ “የዳዊት ልጅ” ተብሏል።