am_tw/bible/names/canaan.md

858 B

ከነዓን፣ ከነዓናዊ

ከነዓን የኖኅ ወንዶች ልጆች አንዱ የነበረው የካም ልጅ ነበር። ከነዓናውያን የከነዓን ዘሮች ናቸው።

  • “ከነዓን” ወይም “የከነዓን ምድር” የሚለው ቃል በዮርዳኖስ ወንዝና በሜዲትራንያን ባሕር መካከል የነበረውንም ቦታ ወይም አካባቢ ያመልክታል። በስተ ደቡብ በኩል እስክ ግብፅ ዳርቻና በስተ ሰሜን እስከ ሶርያ ዳርቻ ይደርሳል።
  • በዚያ ምድር ከንዓናውያንና ሌሎችም በርካታ ሕዝቦች ይኖሩ ነበር።
  • የከነዓንን ምድር ለአብርሃምና የእርሱ ዘሮች ለሆኑት እስራኤላውያን እንደሚሰጥ እግዚአብሔር ቃል ገብቶአል።